Tuesday, February 4, 2014

በደቡብ እና ምስራቅ ኢትዮጵያ አሰቃቂ ረሀብ መከሰቱ ተዘገበ

አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በመጥቀስ እንደዘገቡት በደቡብ እና ምስራቅ ኢትዮጵያ አስከፊ ረሀብ መከሰቱን ተከትሎ የህዝቡ ህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል። የሲኤን ቢሲ ዘጋቢ እንደገለጸው ችግሩን ለመቅረፍ እስከ 100 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ ያስፈልጋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የያዘው የምግብ ክምችት ማለቁንም በዘገባው ተገልጿል። እንደ ሲኤን ቢሲ ዘገባ በአፍሪካ ወደ 14 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ የሚፈልግ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ ወደ 10 ሚሊዮን የሚጠጋው ኢትዮጵያዊ ነው።
የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ተፈራ ደርበው ሰሞኑን በፓርላማ ተገኝተው ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጸው የነበረ ቢሆንም ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግን አፋጣኝ ምግብ የሚፈልጉ ሰዎችን ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን አድርሶታል።
http://ethsat.com/amharic/

No comments:

Post a Comment