Thursday, December 5, 2013

የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ካድሬዎቻቸው በፓስፖት እና በቀበሌ መታወቂያ ንግድ ላይ ተሰማርተው እንደነበር ተገለፀ።

የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ካድሬዎቻቸው በፓስፖት እና በቀበሌ መታወቂያ ንግድ ላይ ተሰማርተው እንደነበር ተገለፀ።
 
ሰሞኑንን ኢ.ቲ.ቪ አይናችን በሚል ፕሮግራሙ ባሰራጨው በዚህ ስፊ ዘግባ ላይ የኢሚግሬሽን እና ስደተኞች ጉዳይ መምሪያ መቤ/ት እና የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት መዋቅር እንደሆኑ የሚነገርላቸው ቀበሌዎች ውስጥ የተሰማሩ ካድሬዎች በመታወቂያ እና በፓስፖርት ህገወጥ ስራ ላይ ተሰማርተው እንደነበር ከቀረበው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። 
በአንድ ቤት እስከ 40 መታወቂያ የሚወጣበት አጋጣሚ መኖሩን በተጨባጭ፡ያረጋገጠው የፕሮግራሙ አዘጋጅ የኤምግሬሽኝ እና ስደተኞች ጉዳይ መመሪያ ሃላፊዎች ለውጭ፡ሃገር ዜጎች ፓስፖርት በመሸጥ የአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎችን ከፍተው አያሌ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን ወደ አረብ ሀገር በመላክ ለሞት እና ለስቃይ መዳረጋቸውን ጸሃይ የሞቀ የአደባባይ ሚስጥር መሆኑ ቢታወቅም ኢቲቪ የተጠቀሱትን ባለስልጣኖች በግርድፉ የህገሪቱን ሰነድ አሳልፈው የሸጡ ብሎ አድበስብሷት አልፎል። 
እንደሚታወቀው ከዛሬ 4 አመታት በፊት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት ለሳውዲ አረቢያ የቤት ሰራተኛ ለማቀረብ በገባው ውል መስረት አንዳንድ ከፍተኛ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ባለስልጣናት በውጭ፡ሃገር ዜጎች ስም በእጅ አዙር ሰራተኛ እና አስሪ ኤጀንሲዎችን ከፍተው ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ተጓዥ እስከ 7መቶ ዶላር በማስከፈል በወር ከ 45 ሺህ ያላነሱ እድሜያቸው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ኢትዮጵያውያንን ህጻናት እህቶቻችንን ጭምር ያለምንም የህይወት ዋስትና ወደ ሳውዲ አረቢያ በመላክ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ.መንግስት ባወጣው ህግ ሸፋን በወገኖቻችን ደም ንግድ ላይ ተሰማርተው መኖራቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ ። የሳውዲ አረቢያ መንግስት ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ወደ ሃገሩ እንዳይገቡ የመግቢያ ቪዛ ማገዱን ተከትሎ የኢትዮጵያ መንግስት የተጠቀሱትን ኤጀንሲዎች ላልተወሰነ ግዜ መዝጋቱን ለማረጋገጥ ተችሏል። 
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

No comments:

Post a Comment